Getayen Bekaskut

ሐጥያት በደሌን ትቼ
በፍቅር ወደርሱ መጥቼ
በእንባዬ እግሮቹን ባጠብኩት
ብቻ ጌታዬን በካስኩት

ነፍሴን እያሳደፍኩ በበደል ስኖር
ለካ ሳፈርስ ነበር ሕንፃ እግዚአብሔር
አሁን ግን አንጽድቶኝ በልቤ በገባ
እሰዋለታለሁ የእንባዬን መባ
አዝ
ድካሜን ሳይቆጥር ጌታዬ ከጠራኝ
ወደኋላ አላይም ከእንግዲህ ምን አለኝ
መቅጫዬን ትቼ እከተለዋለሁ
ከእርሱ ጋራ ውዬ ከእርሱ ጋር አድራለሁ
አዝ
ምሬሀለሁ ብሎ ካበዛልኝ ፀጋ
እለዋለሁ ቅዱስ ሲመሽም ሲነጋ
ፍቅሩ በልቤላይ ስሙ በአንደበቴ
ዘወትር አይጠፋም እርሱ ነው ጉልበቴ
አዝ
ልጄ ብሎ ጠራኝ እጆቹን ዘርግቶ
እርሱን ማሳዘኔን በደሌን እረስቶ
በፍታን አለበሰኝ ፍሪዳን አረደ
የፈጠረኝ ጌታ መዳኔን ወደደ
አዝ



Credits
Writer(s): Simone Tsegay
Lyrics powered by www.musixmatch.com

Link