Silemihiretu

ስለ ፡ ምህረቱ ፡ ስለ ፡ እርሱ ፡ ዝና
ሰምቼ ፡ መጣሁ ፡ ሁሉን ፡ ተውኩና
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ አዩት ፡ ዐይኖቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሕይወት ፡ አግኝቼ
ስለ ፡ ምህረቱ ፡ ስለ ፡ እርሱ ፡ ዝና
ሰምቼ ፡ መጣሁ ፡ ሁሉን ፡ ተውኩና
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ አዩት ፡ ዐይኖቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሕይወት ፡ አግኝቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሰላም ፡ አግኝቼ

ነፍሴ ፡ የወደደችው ፡ እርሱን
አይሆንላትም ፡ ሌላ ፡ ነገረ
ከእርሱ ፡ ጋራ ፡ ይዟታል ፡ ፍቅር
የለም ፡ አለች ፡ ከቶ ፡ እንደእግዚአብሔር
ቸርነቱ ፡ ምህረቱ ፡ የበዛ
አይገኝም ፡ የለም ፡ እንደጌታ

አየሁ ፡ ምህረቱን ፤ አየሁ ፡ ቸርነቱን
አየሁ ፡ ለተጠጋው ፤ አየሁ ፡ ሰው ፡ መውደዱን
አየሁ ፡ ሁልጊዜ ፤ አየሁ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
አየሁ ፡ እንደማይተወኝ ፤ አየሁ ፡ ስም ፡ ሲፈራ
አየሁ

ለጌታ ፡ ለቸርነቱ ፤ ለጌታ ፡ ምሥጋናን ፡ አምጡ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ ለጌትነቱ
ለጌታ ፡ ይዘመርለት ፤ ለጌታ ፡ ይሁን ፡ ምትሉ
ለጌታ ፡ ለቸሩ ፡ ጌታ ፤ ለጌታ ፡ እስኪ ፡ እልል ፡ በሉ
ለጌታ ፡ ከዚህም ፡ በላይ ፤ ለጌታ ፡ ለእርሱ ፡ ቢሰዋ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ አዳኝ ፡ ነውና

ስለ ፡ ምህረቱ ፡ ስለ ፡ እርሱ ፡ ዝና
ሰምቼ ፡ መጣሁ ፡ ሁሉን ፡ ተውኩና
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ አዩት ፡ ዐይኖቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሕይወት ፡ አግኝቼ
ስለ ፡ ምህረቱ ፡ ስለ ፡ እርሱ ፡ ዝና
ሰምቼ ፡ መጣሁ ፡ ሁሉን ፡ ተውኩና
ከሰማሁት ፡ በላይ ፡ አዩት ፡ ዐይኖቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሕይወት ፡ አግኝቼ
እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረሁ ፡ ሰላም ፡ አግኝቼ

ያ ፡ ጠላቴ ፡ ሊያጠፋኝ ፡ ሲያቅድ
በየቀኑ ፡ ወጥመዱን ፡ ሲያጠምድ
ቢሆንለት ፡ ሕይወቴን ፡ ሊያጠፋ
ሳያቋርጥ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ለፋ
ኢየሱሴ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነበረ
የጠላቴም ፡ ወጥመድ ፡ ተሰበረ

አየሁ ፡ ምህረቱን ፤ አየሁ ፡ ቸርነቱን
አየሁ ፡ ለተጠጋው ፤ አየሁ ፡ ሰው ፡ መውደዱን
አየሁ ፡ ሁልጊዜ ፤ አየሁ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
አየሁ ፡ እንደማይተወኝ ፤ አየሁ ፡ ስም ፡ ሲፈራ

ለጌታ ፡ ለቸርነቱ ፤ ለጌታ ፡ ምሥጋናን ፡ አምጡ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ ለጌትነቱ
ለጌታ ፡ ይዘመርለት ፤ ለጌታ ፡ ይሁን ፡ ምትሉ
ለጌታ ፡ ለቸሩ ፡ ጌታ ፤ ለጌታ ፡ እስኪ ፡ እልል ፡ በሉ
ለጌታ ፡ ከዚህም ፡ በላይ ፤ ለጌታ ፡ ለእርሱ ፡ ቢሰዋ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ አዳኝ ፡ ነውና

ለጌታ ፡ ለቸርነቱ ፤ ለጌታ ፡ ምሥጋናን ፡ አምጡ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ ለጌትነቱ
ለጌታ ፡ ይዘመርለት ፤ ለጌታ ፡ ይሁን ፡ ምትሉ
ለጌታ ፡ ለቸሩ ፡ ጌታ ፤ ለጌታ ፡ እስኪ ፡ እልል ፡ በሉ
ለጌታ ፡ ከዚህም ፡ በላይ ፤ ለጌታ ፡ ለእርሱ ፡ ቢሰዋ
ለጌታ ፡ ስለሚገባው ፤ ለጌታ ፡ አዳኝ ፡ ነውና



Credits
Writer(s): Samuel Alemu, Yosef Kassa
Lyrics powered by www.musixmatch.com

Link