Alebegn Tezeta

አዝ፦ እኔ የማይረሳኝ ውለታ
አለብኝ አንድ ትዝታ
ቀራንዮ መስቀሉ ላይ
ሞቶ ያዳነኝ

እኔን ለማዳን ነው የደም ላብ ያላበህ የሞትክልኝ
ተሰቃየህልኝ መርገሜን ወሰድከው ልታድነኝ
ልጅህ ነኝ በጣር የወለድከኝ ሕይወትና ሰላም የሆንከኝ
በሞትህ እኔን ስታድነኝ አየሁ የመስቀሉ ፍቅርህን

(አልረሳውም እኔ) ለኔ የዋልክልኝ አለብኝ ውለታ
(አልረሳውም እኔ) ተሰቃየህልኝ ሞትክልኝ ጎልጎታ
(አልረሳውም እኔ) ዘመኔን በሙሉ አንተን ባመልክህ
(አልረሳውም እኔ) ምክንያቴ ይሄ ነው የመስቀል ፍቅርህ

አዝ፦ እኔ የማይረሳኝ ውለታ
አለብኝ አንድ ትዝታ
ቀራንዮ መስቀሉ ላይ
ሞቶ ያዳነኝ

አምላክ ሆነህ ሳለህ ሲያንገላቱህና ሲያፌዙብህ
እንደወንጀለኛ አስረው ሲገርፉህስ መች ራሩልህ
ሲንቁህ ሲሳበቁብህ ፥ መልስም አልነበረህ ሲወግሩህ
ለኔ ነው ይህ ሁሉ የሆነው ፥ እንዴት እንድትወደኝ እንዳየው

(አልረሳውም እኔ) ለኔ የዋልክልኝ አለብኝ ውለታ
(አልረሳውም እኔ) ተሰቃየህልኝ ሞትክልኝ ጎልጎታ
(አልረሳውም እኔ) ዘመኔን በሙሉ አንተን ባመልክህ
(አልረሳውም እኔ) ምክንያቴ ይሄ ነው የመስቀል ፍቅርህ

ለኔ ነው ለኔ
በመስቀል ላይ የሞተው ስለኔ



Credits
Writer(s): Simone Tsegay
Lyrics powered by www.musixmatch.com

Link