Weletaw Alebegn

አዝ፦ ያደረገልኝን ውለታውን
ሳስብ ለእኔ የሆነውን
አመስግን ይለኛል እንደገና
ውስጤ ይጮህብኝና

ከየት እንደተነሳሁ የሆነልኝ ትዝ አለኝና
በአምላኬ ፊት ጨፈርኩኝ ደስ እያለኝ ክብሬን ተውኩና
እንዳበደ ቢያዩኝ በልባቸው ቢንቁኝ
ልቤ አምላኬ ላይ ነው ምንም ቢሆን መች ትዝ አሉኝ [1]

ምህረቱን (እንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
ቸርነቱን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
ጥበቃውን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
አባትነቱን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)

ከሆንኩለት በላይ ልሁንለት
ራሤን ባዋርደው አለኝ ምክንያት
ሥርዓትስ ቢሉኝ መች ሊገባኝ
ውለታውን ሳስብ ይብስብኝ

ያደረገልኝን ውለታውን
ሳስብ ለኔ የሆነውን
አመስግን ይለኛል እንደገና
ውስጤ ይጮህብኝና

ኢየሱስ አለ ሲሉኝ ሮጬ መጣሁ ሽቶዬን ይዤ
ፊቱን ሳየው ሰገድኩኝ እግሩን ልሳም ይራስ በእምባዬ
ምን ነካው አትበሉኝ አምላኬ ነው እስኪ ተዉኝ
ብዙ ምህረት ያገኘሁ ይቅር የተባልኩ ሰው ነኝ [2]

ምህረቱን (እንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
ቸርነቱን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
ጥበቃውን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)
አባትነቱን (አንደ እኔ ያየ) ልቡ ተነሳ (ላምልከው አለ)

ከሆንኩለት በላይ ልሁንለት
ራሤን ባዋርደው አለኝ ምክንያት
ሥርዓትስ ቢሉኝ መች ሊገባኝ
ውለታውን ሳስብ ይብስብኝ

ብቀኝለትም ብሰግድለትም ባሸበሽብም (ለእርሱ)
ህይወት ለሆነኝ ሰላም ለሰጠኝ ከሞት ላዳነኝ (ለእርሱ)

ውለታው (አለብኝ እኔ)



Credits
Writer(s): Simone Tsegay
Lyrics powered by www.musixmatch.com

Link